የባቱ – አርሲ ነጌሌ ግንባታ
ሞጆ 🛣 ሀዋሳ !
👉 በእስራኤሉ SBI international holdings A.G /ኤስ ቢ አይ ኢንተርናሽናል ሆልዲንግስ ኤ.ጂ ነው/ የሚነናወነው።
👉 የማማከርና ቁጥጥር ስራውን ኩንውሀ ኢንጂነሪንግ እና ኮንሰልቲንግ ከኮሪያ ኤክስፕረስ ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ እያከናወኑ ነው።
👉 ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ የሚሆነው ሶስት ቢሊየን ሶስት መቶ አምስት ሚሊየን ሁለት መቶ አርባ ሶስት ሺህ ብር እየተሸፈነ የሚገኘው ከአለምባንክ በተገኘ ፋይናንስ ነው፡፡
👉 የአፈር ቆረጣ ስራ፣ ሰብ ቤዝ ስራዎች፣ የስትራክቸር ፣የውሀ ማፋሰሻ ፣ የአቃፊ ግንብ፣ ትላልቅ የድልድይ ግንባታ፣ ማሳለጫዎችና ማቋረጫዎች እና የክሬሸር ስራ በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
👉 21 ኪ.ሜ የDBM/ ለመጨረሻ የአስፋልን ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ ተጠናቋል/ ።
አርሲ ነጌሌ – ሀዋሳ የሚዘልቀው የመንገድ ክፍል ፦
👉 ሚገነባው የስራ ተቋራጭ cccc ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ነው።
👉 የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ቤጂንግ ኤክስፕረስ ዌይ ሱፐር ቪዥን ካምፓኒ ሊሚትድ ከውሀን ጄአይኦኬ ኢንጅነሪንግ ኮንሰልታንሲ ሊሚትድ ጋር በጋራ በመሆን እየሰሩት ነው ፡፡
👉 መንገዱን ለመገንባት የሚውለውን ወጪ አምስት ቢሊየን አንድ መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ብር በቻይናው ኤግዚም ባንክ 85 በመቶ እና 15 በመቶ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡
👉 በአርሲ ነጌሌ – ሀዋሳ የመንገድ ፕሮጀክት የአፈር ቆረጣ እና ድልዳሎ ስራ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣የስትራክቸር ስራዎች፣ የሰብ ቤዝ ስራ፣ የውሀ ማፋሰሻ ቱቦዎች ቀበራ ፣ የድልድይ ግንባታ፣ የጠጠር ንጣፍ ስራዎች እየተሰሩ ናቸው፡፡
👉 የ3 ነጥብ 4 ኪ.ሜ ለመጨረሻ የአስፋልት ንጣፍ ስራ ዝግጁ የማድረግ ስራ የDBM ተጀምሯል።



Read more Articles
https://constructionproxy.com/ethiopian-construction-update-and-articles